Weight | 168 g |
---|
ልጆችን በዲን ማሳደግ
3.00 $
ሙስሊም የሆነ ሰው የኢስላም መርሆዎችን በቅጡ መረዳት ይኖርበታል፤ በተለይ የእምነቱን ምንነት፣ መልካምነትን፣ የምድር ላይ ኃላፊነትን በሚገባ ሊያውቅ ይገባል፡፡ ይህንኑ ዕውቀቱንም ለልጆቹ ሊያወርስ ይገባል፡፡ አንድ ወላጅ ለልጁ ከሚያወርሰው ነገር ሁሉ ዉዱ ነገር ተሻጋሪ የሆነው ዲን ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ይህ መጽሐፍ አንድ ወላጅ የተለያዩ ተጽኖዎችን ቋቁሙ ልጆቹን እንዴት እርከን በእርከን አድርጎ ልጆቹን በዲን እና በመልካም ማሳደግ እንዳለበት ይጠቁማል፡፡
ዝግጅት ፡ ዶ/ር ዓኢሻ ሐምዳን
ትርጉም ፡ ዐብዱልከሪም ታጁ
የገጽ ብዛት ፡ 188
የታተመበት ዓመት ፡ ሰኔ 2006
ከመጽሐፉ ፡
እንዳለመታደል ሁኖ በዘመናችን አብዛኞቹ ወላጆች በዚህ ፈተና (አላህ በሰጣቸው ፀጋ) ሲወድቁ ወይም ከፈተናው ለማምለጥ ሲሸሹ ይታያል። ልጆቻቸው ብዙ ጊዜያቸውን በልጆች ማቆያ ውስጥ እንዲያሳልፉ ያደርጓቸዋል። ወይም አካላዊና ሥነ-ልቦናዊ ፍላጎቶቻቸውን እንዲያሟሉላቸው ሞግዚት ይቀጥሩላቸዋል። ለሥራ፣ ለገንዘብ፣ ለጓደኝነትና ለመዝናናት ቅድሚያ ስለሚሰጡ ብዙ ጊዜያቸውን ለግንኙነቶቻቸውና ፕሮጀክቶቻቸው ይወስዱባቸዋል። ለልጆቻቸው የሚተርፍ ጊዜ የላቸውም። ልጆች ትኩረት አይሰጣቸውም። እዚህ ላይ ወላጆች ያልተገነዘቡት ትልቅ ነገር፣ ለልጆቻቸው በቂ ጊዜና ትኩረት ባለመስጠታቸው ምክንያት በፀጋ መልክ በቀረበላቸው ፈተና እየወደቁ መሆናቸውንና በዚህ ፈተና በመውደቃቸው ምክንያት ደግሞ ዘላለማዊና የማይጠወልግ ዕድል እያመለጣቸው መሆኑን ነው።
አሳታሚ ፡ ነጃሺ ማተሚያ ቤት